ልጥፎች

“ወደ ሠርግ ገቡ።” (ማቴ 25 ፣ 10)

ምስል
፩ ቆሮ ፯፥ ፳፭-ፍ፡ም ፤ ፪ ዮሐ፡ ም. ፩፥ ቍ. ፩-፮፤ ሐዋ. ፲፮፥ ቍ. ፲፫-፲፰፤ መዝ፡ ፵፬(፵፭)፥  ፱-፲። ማቴ ፳፭፥ ፩-፲፱  የዛሬ ምንባባት ሠርግ፣ ጋብቻ፣ ቤተሰብ የሚሉ ነጥቦች ተደጋግመው ይሰሙባቸዋል። ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ጋብቻና ስለ ትዳር የለሽነት ይመክራል። ቅዱስ ዮሐንስ በፍቅር ኑሮ በሚገለጠው የኢየሱስ ክርስቶስን በሥጋ መገለጥ የማመን ሐዋርያዊ እምነት ይጠቁማል። ከሐዋርያት ሥራ የተመረጠው ምንባባችንም ለቤተሰቧ ኹሉ ምክንያተ ድኅነት ስለኾነችው ስለልባሚቱ ሴት ስለልድያ ይተርካል። ምስባኩ “የንግሥት ልጆች ለክብርኽ ናቸው። ንግሥቲቱም ወርቅ ለብሳና ተጎናጽፋ በቀኝኽ ትቆማለች።” ብሎ ስለ ቤተሰባዊ የንጉሡ ክብር ቤተሰባዊ መልክ ምን እንደሚመስል ያሳየናል። ቅዱስ ማቴዎስም ጌታችን ኢየሱስ መንግሥተ ሰማያትን በሠርግ መስሎ ሲያሰተምር አሰምቶናል። ሠርግ፣ ትዳር፣ ቤተሰብ። ይኽ ከእመቤታችን በዓለ ዕረፍት ወፍልሰት ጋር ምን ያገናኘዋል? እስኪ ወደ፣ ሠርግ እና ገቡ የሚሉትን ሦስት ቃሎች ከጌታችን ምሳሌ እንውሰድና ጉዳዩንም ራሳችንንም እንመልከተው።  ወደ  “ወደ” የሚለው ቃል እንቅስቃሴን ያመለክታል። “ወደ” የሚል ቃል ስንሰማ መድረሻውን እንጠብቃለን። ምናልባትም የሰውን ልጅ አጠቃላይ ምድራዊ ኑሮ ያመለክታል። የሰው ምድራዊ ኑሮ በአንድ ቃል ይጠቅለል ከተባለ “ወደ” ሳትገልጸው አትቀርም። ሲፈጠርም ወደ ተደርጎ ነው።  የሰው ልጅ ተጓዥ ነው። ዋሻ ውስጥ እንኳ ዘግቶ ቢቀመጥ ከመጓዝ አያመልጥም። እርሱ ቢቆም እንኳ ጊዜ ተሸክሞት ይኼዳል። ወደደም ጠላም በዚኽ ምድር ላይ ሰው በማያቋርጥ ጉዞ ላይ ነው። እስከ መጨረሻዋ እስትንፋሱ ድረስ እየኾነ ይኼዳል እንጂ ኾኖ አይቆምም። እየኾነ ነው። እየተጓዘ ነው። በአእምሮው ውስጥ የሚኖረው የተሳፈረበት የጊዜ ባቡር ይዞት

“ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቷችኋል።”

፪ኛ፡ ቆሮ፡ ም. ፱፥ቍ. ፮-ፍ፡ም፤ ያዕ፡ ም. ፫፥ቍ. ፲፫-ፍ፡ም፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፳፯፥ቍ. ፳-፳፮፤ ማቴዎስ፡ ም. ፲፫፥ ቍ. ፲፰-፳፬  ከሠኔ 25 እስከ መስከረም 25 ያለው ጊዜ ዘመነ ክረምት ይባላል። የዛሬ ምንባቦችም ክረምት፣፣ ዘር መዝራት፣ ፍሬ መስጠት የሚሉ ጭብጦችን ያነሣሉ። መዝሙረኛው እግዚአብሔርን “ለእንስሳት ሣርን የሚያበቅል፣ የሰውንም እርሻ በልምላሜና በፍሬ ባርኮ የሚመግብ እንደኾነ እያነሣ እግዚአብሔርን በመጋቢነቱ ያመሰግናል።  ቅዱስ ጳውሎስ የቆሮንቶስን ምእመናን ሀብቱን ለድኾችና ለችግረኞች የቤተ ክርስቲያን አባላት የዘራ ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ ዕጥፍ ድርብ በረከት እንደሚቀበል እየነገረ የልግስናን ገበሬዎች ያበረታታል። ቅዱስ ያዕቆብም ሰው በልቡ ውስጥ የእግዚአብሔርን ጥበብ ቢዘራ ንጽሕና፣ ዕርቅ፣ ገርነት፣ ትሕትናን፣ ምሕረትን እንደሚያበቅል ይናገራል። ሰው በልቡ ውስጥ የአጋንንትን ጥበብ ቢዘራ ደግሞ ቅንዓት፣ አድመኛነት፣ ሑከት፣ ክፉ ሥራ ሁሉ እንደሚበቅሉበት በግልጽ ያስተምራል። የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚታዩት ፍሬዎች የትኞቹ ናቸው? በአጥቢያችን የሚታዩት ፍሬዎችስ የትኞቹ ናቸው? በእኔ ሕይወት ውስጥ የሚታዩት ፍሬዎችስ? ከአንደበታችን የሚወጣው፣ ከአኗኗራችን የሚንጠባጠበው ፍሬ በልባችን ውስጥ የማንን ጥበብ ዘርተን እንደምንኖር ይመሰክርል/ብናል። የሐዋርያት ሥራ ምንባብ ደግሞ በልቡ የእግዚአብሔር ጥበብ የኾነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የዘራው ገበሬ ቅዱስ ጳውሎስ በእሥረኝነት ኾኖ አሣሪዎቹን ሲያጽናና ያሳየናል። የወንጌል ምንባባችንም ጌታ ኢየሱስ የዘሪውን ምሳሌ ለደቀ መዛሙርቱ ሲያብራራላቸው እንመለከታለን። በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ጌታ ኢየሱስ ይኽን ማብራሪያውን የሚጀምረው ግን ዛሬ ከተነበበው ክፍል ጥቂት ከፍ ብሎ ነው። እንዲኽ ይላል

“የለንም!”

ምስል
ምንባባት፦ ሮሜ ፬፥ ቊ. ፲፬-ፍ፡ም፤ ራእ ፳፥ ፩-ፍ፡ም ፤ ሐዋ ፲፥ ፴፱-፵፬ ፤ መዝ ፸፯(፸፰)፥ ፳፱-፴ ፤ ዮሐ ፳፩፥ ፩-፲፭ ።   የዛሬው ወንጌል ቢያንስ ሦስት መሠረታዊ የክርስትና ምሥጢሮችን ይነግረናል።  ትንሣኤና ፍቅር   በዛሬው ወንጌል ውስጥ ከምናያቸው ነጥቦች መካከል አንዱ ጌታ ኢየሱስ ከትንሣኤው በኋላ ሥልጣኑን፣ ወይም ትክክለኛነቱን ለማሳየት ከሃይማኖት ተቋማቸው የሚያገኙትን ጥቅም፣ ክብርና ምቾት ለማስጠበቅ ሲሉ ወደገደሉት ካህናትና መምህራን ወይም ፖለቲካዊ ሥልጣኑን ለማስጠበቅ ሲል በግፍ እንዲሰቀል አሳልፎ ወደ ሰጠው ወደ ጲላጦስ ሥልጣኑን ሊያሳያቸው፣ እውነተኛ መሢሕነቱን እግዚአብሔር ከሞት በማስነሣት እንደገለጠ በመመስከር ሊያሳፍራቸው አልኼደም። “እኔ ትክክል ነበርኹ እናንተ ግን ስሕተተኞች፣ ወንጀለኞች ናችኹ” አላላቸውም። ክብሬ ተነካ የምትል አተካራ በእርሱ ዘንድ የለችም። ምክንያቱም እርሱ የሰው ክብር አይፈልግም (ዮሐ 5፡ 42)። ይልቁንም ወደሚወድዱት፣ ወደሚናፍቁት፣ እርሱን በማጣታቸው ሕይወታቸው ወደ ተመሰቃቀለባቸው፣ የትንሣኤውን ዜና ሲሰሙ ደግሞ ግራ ወደ ተጋቡት ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣ። የዛሬው ወንጌል የሚነግረን ጌታ ኢየሱስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ እንደተገለጠላቸው ነው። እስከሞት ድረስ የወደዳቸውን ወዳጆቹን ከትንሣኤው በኋላም “በቃ፣ ሥራዬን ጨረስኹ!” የራሳችኹ ጉዳይ ብሎ ጥሏቸው አልኼደም። በፍርኀት ቤት ዘግተው ሲቀመጡ የተዘጋ ቤት ውስጥ ገብቶ፣ ጥርጥር በልባቸው ሲሰፍን እጆቼንና እግሮቼን ዳስሱኝ ብሎ፣ ትንሣኤውን በማመን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠውን የዘለዓለም ተስፋ ላይ ልባቸውን እንዲያሳርፉ ደጋግሞ ታይቷቸዋል። ዛሬ እንደተነበበልን ደግሞ ኹልጊዜም ከእነርሱ ጋር እንደኾነ፣ ድካማቸውን እንደሚያውቅ፣ ችግራቸውን እንደሚረዳ አ

ትንሣኤ ስም እና ቅድስና

ምስል
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን! በአማን ተንሥአ! የዕለቱ ምንባቦች፦ ፩ኛ፡ ቆሮ፡ ም. ፲፭፥ ቊ. ፩-፳፤ ፩ኛ፡ ዮሐ፡ ም. ፩፥ቊ. ፩-ፍ፡ም፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፳፫፥ ቊ. ፩-፲፤ ዮሐንስ፡ ም. ፳፥ቊ. ፲፱-ፍ፡ም፤ ዮሐንስ፡ ም. ፲፯፥ ቍ. ፩-ፍ፡ም። ትንሣኤ  የበዓላት ኹሉ በኵር፣ የቤተክርስቲያን ትርጉምና ድሏ የሙሽራዋ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው። ስለዚኽም፣ ከበዓላት ኹሉ ከፍ አድርጋ ትንሣኤን ታከብራለች። በክርስቶስ ትንሣኤ ውስጥ ያለውን ደስታ፣ ተስፋና ሕይወት በሚገባ እንድናጣጥመውም ስምንት ቀናትን እንደ አንድ ቀን ቆጥራ ስታከብር፣ እርሱም አልበቃ ብሎ እስከ ዕርገት በዓል ድረስ ያሉትን 40 ቀናት ስትጨምርበት እናያታለን። ለምን? ምክንያቱም የክርስቶስ ትንሣኤ እውነት ካልኾነ ቤተክርስቲያን ከንቱ ናት። የነቢያት ትንቢት፣ የሐዋርያትም ስብከት፣ የሰማዕታት መከራ፣ የእናንተም ጾምና ጸሎት የመቃብር ድንጋይ ደፍጥጦ በዜሮ የሚያባዛው ከንቱነት ይኾናል። ሰው ኾኖ መኖርም ትርጉም የሌለው የመከራ ቀንበር ይኾናል። ግን ክርስቶስ በእውነት ከሙታን ተነሥቷል ስለዚኽም ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፣ “ በኹሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ኹልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን። ” (2ኛ ቆሮ. 4፡8) ኹልጊዜ በጌታ ደስ ይለናል! (ፊል 4፡4)      ስም ይኽ ዛሬ ከዮሐንስ ወንጌል የተነበበው ምንባብ የጌታ ኢየሱስ የሊቀ ካህንነቱ ( כהן גדול) ( ἀρχιερεύς) ጸሎት ይባላል። ከዚኽ ጸሎት ቀጥሎ የሚመጣው የዓለሙን ኃጢኣት የሚያስወግደው የእግዚአብሔር በግ የተቀበለው መከራ ነው። በዚኽ ጸሎት ጌታ ኢየሱ

“ዓለም በልጁ እንዲድን እንጂ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውም” (ዮሐ 3፡17)

ምስል
የዕውቀት ድንበር፣ ከላይ መወለድና የፍቅር ነጻነት  ምንባባት፦ ሮሜ 7፡1-19፤ 1ኛ ዮሐ 4፡ 18-ፍጻሜ፤ ሐዋ 5፡ 34-ፍጻሜ፤ መዝ 16(17)፣ 3፤ ዮሐ 3፡ 1-20።   ዐቢይ ጾም ከተጀመረ ሰባተኛ ሳምንት ላይ ደረስን። ይኽ ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል። ቤተ ክርስቲያን ኒቆዲሞስ ለተሰኘው በጌታ መዋዕለ ሥጋዌ ለነበረ መምህር የተሰጠውን ምሥጢረ ጥምቀትን የሚመለከት ትምህርት እያስታወሰች፣ ደግሞም ኒቆዲሞስ ሲጀምር በጨለማ ቢመጣም ኋላ ላይ ጌታን አምኖ ያደረገውን በጎ ምግባር እየዘከረች በጾመ ድጓዋ ሙሽራዋን በኒቆዲሞስ አንደበት “ረቢ ንብለከ፤ ነአምን ብከ” (መምህር እንልኻለን፤ እናምንብኻለንም) እያለች ትዘምራለች።  በጥንቱ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ዐቢይ ጾም ንዑሰ ክርስቲያን በፋሲካ ሌሊት ለሚካኼደው ጥምቀታቸው የሚዘጋጁበት ጊዜ ነበረ። ስለዚኽ የጥምቀት ጊዜያቸው ከመድረሱ ጥቂት ቀደም ብሎ ይኽን ምሥጢረ የሚመለከት ትምህርት መማራቸው የሚገባ ነው። ከእነዚኽ ምንባቦች ውስጥ ሦስት ነጥቦችን እናንሳና ራሳችንን እንመልከት።        የዕውቀት ድንበር  ዛሬ በምንባቦቹ ውስጥ ያገኘናቸው ኒቆዲሞስና ገማልያል የሚባሉ መምህራን በማመንና ባለማመን ድንበር ላይ ቆመው እናገኛቸዋለን። የሚያዩትን ጌታ ኢየሱስ የሚባል እውነት፣ በትምህርት ከሚያውቁትና ይኾናል ብለው ከሚጠብቁት ለማስማማት የቸገራቸው ይመስላል። ገማልያልም የሐዋርያትን ስብከት ለተቃወመው የአይሁድ ሸንጎ “ይህ ሥራ ከሰው እንደሆነ ይጠፋል፤ ከእግዚአብሔር እንደሆነ ግን ታጠፏቸው ዘንድ አይቻላችኹም” ብሎ ያሳስባል። “እንደኾነ”ን ከሥሯ እናሥምርባት። ኒቆዲሞስ ደግሞ ሰው በማያይበት፣ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ “መምህር ኾነኽ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣኽ እናውቃለን” ብሎ ዕውቀቱን ይገልጣል። ኹለቱም መምህራን

“በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻ አወጣን።”

ምስል
ገላትያ 5፡1፤ ያዕቆብ 5፡ 14 ፤ ሐዋ 3፡ 1፤ መዝ 40፡ 3 ፤ ዮሐ. 5፡ 1  የዐቢይ ጾም አራተኛ ሳምንት ላይ ነን። መጻጕዕ ይባላል። ይኽ ሳምንት ጌታ ኢየሱስ ድውያንን መፈወሱን የምታስብበት ነው። በጾመ ድጓዋ “ብውሕ ሊተ እኅድግ ኃጢኣተ በዲበ ምድር፤ እስብክ ግዕዛነ፣ ወእክሥት አዕይንተ ዕውራን፤ አቡየ ፈነወኒ።” (በምድር ላይ ኃጢኣትን ይቅር እል ዘንድ፣ ነጻነትን እሰብክ ዘንድ፣ የዕውራኑን ዓይኖች እከፍት ዘንድ አባቴ ላከኝ) እያለች ወልድ ከአብ ዘንድ ተልኮ ነጻ ያወጣን ዘንድ እንደመጣ ትዘምራለች። በወንጌል የተጠቀሱትን የጌታ የፈወሳቸውን እየጠቃቀሰች ታዜማለች። ከደስታዋም ብዛት “በሰንበት ፈወሰ ዱያነ፤ ወከሠተ አዕይንተ ዕውራን በሰንብተ፤ ፈድፋደ ኪያነ አፍቀረነ።” (በሰንበት ሕሙማንን ፈወሰ፤ የዕውራኑን ዓይኖች ከፈተ፤ እኛን እጅግ ወደደን!) ትላለች። በዚኽ እሑድ የሚነበቡት ምንባባትም ኹሉ ስለ ሕመም፣ ስለ ፈውስ እና ስለ ነጻነት ይናገራሉ። ዋናው ጉዳይ ግን መታመም ወይም መፈወስ ሳይኾን እግዚአብሔር በአንድ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በሠራውና ዛሬም አካሉ በኾነችውና መንፈሱን በለበሰችው ቤተክርስቲያኑ በሚሠራው ሥራ ለሰው ልጅ የሰጠው ዘለዓለማዊ ግዕዛን (ነጻነት) ነው። በዚኽ አጀንዳ ላይ ሰዎች የእግዚአብሔርን ሐሳብ ምን ያኽል እንደማይረዱት በዮሐንስ ወንጌል 5 ላይ ያለው ለ38 ዓመታት ታምሞ የኖረው ሰው ታሪክ በግልጽ ያሳያል። በዚኽ ታሪክ ውስጥ ሦስት የተለያዩ አካላትን እንመለከታለን።    አንድ፦ ታማሚው ሰው  ታማሚው ሰው 38 ዓመት በሥቃይ ኖሯል። ተንገላትቷል። ፈውስ ጠብቆ አላገኘም። ሮጦ መያዝ፣ ሠርቶ መክበር፣ ሌሎች ሰዎች የሚያደርጉትን ማድረግ አልኾነለትም። ስለዚኽ፣ “ከሰዎች አንሻለኹ! ስላነስኹም እኔን የሚወድደኝ የለም። ሰው የለኝም!” ብሎ

መብዛት፣ መጾም እና መቀደስ

ምስል
  “ከፊት ይልቅ ትበዙ ዘንድ በጌታ በኢየሱስ እንለምናችኋለን።” ኤፌ 4፡ 11 “ περισσεύητε” ፩ ተሰ ም. ፬፥ ቍ. ፩-፲፫ ፤ ፩ ጴጥ፡ ም. ፩፥ ቍ. ፲፫-ፍ፡ም ፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፲፥ ቍ. ፲፯-፴ ፤ መዝሙር፡ ፺፭(፺፮)፥ ቍ. ፭-፮። ማቴዎስ፡ ም. ፮፥ ቍ. ፲፯-፳፭ የዐቢይ ጾም ኹለተኛ ሳምንት ላይ ነን። ሳምንቱ ቅድስት ይባላል። ከዚኽ ሳምንት ጀምሮ እስከ ሆሳዕና ድረስ ያለው ጊዜ "ጾመ አርብዐ"፣ "ጾመ ኢየሱስ" ይባላል። ለዚኽ እሑድ የተመደቡት ምንባቦች ኹሉም ቅድስና ምን እንደኾነ፣ ለሰው ልጅ ምን ያኽል አስፈላጊ እንደኾነና የቅዱስ ሰው ኑሮም ምን መልክ እንዳለው ይናገራሉ። መዝሙረኛው “ምሥጋናና ውበት ሰማያትን በሠራው በእግዚአብሔር ፊት፣ ቅድስናና ግርማም በመቅደሱ ውስጥ እንደኾኑ” ይዘምራል። ጌታ ኢየሱስም “ስትጾሙ እንደግብዞች አትኹኑ!” እያለ የእግዚአብሔር ሕዝብ ጾም ምን እንደሚመስል ያስተምራል። ቅዱስ ጳውሎስ “የእግዚአብሔር ፈቃድ የእናንተ መቀደስ ነው” ይላል። ቅዱስ ጴጥሮስ “በኑሯችኹ ኹሉ ቅዱሳን ኹኑ” ይላል። የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊው ቅዱስ ሉቃስም በምጽዋቱና በጸሎቱ የሚታወቀው መቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ ቅድስናው ይጨምር ዘንድ ጴጥሮስን 40 ማይል ገደማ ርቃ ከምትገኘው ከኢዮጴ ልኮ ሲያስመጣ ሰምተናል። ጾመ ድጓውም “ሰንበትየ ቅድስትየ” እያለ ሰንበትን ከማሞካሸት በተጨማሪ “ተፋቀሩ፡ በምልዓ፡ ልብክሙ። አክብሩ፡ ሰንበተ፡ በጽድቅ፡ ዝግቡ፡ ለክሙ፡ መዝገበ፡ ዘበሰማያት፡ ኀበ፡ ኢይበሊ፡ ወኢይማስን” (በፍጹም ልባችኹ ተፋቀሩ። ሰንበትን በጽድቅ አክብሩ። በሰማያትም ብል የማይበላውና የማይጠፋ ሀብትንን ሀብትን አከማቹ) እያለ እነዚኽኑ ምንባቦች ይዘምራል። እነዚኽን ኹሉ ምንባቦች መብዛት፣ መጾም እና መቀደስ በሚሉ ሦ