ልጥፎች

ከጃንዋሪ, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የደነደነ ልብ፣ የታወረ ዐይን፣ የተሰቀለ መሢሕ

ምስል
የዛሬ የግጻዌ ምንባቦች፦ ፩፡ ቆሮ፡ ም. ፪፥ ቍ. ፩-ፍ፡ም ፤ ፩፡ ዮሐንስ፡ ም. ፭፥ ቍ. ፩-፮ ፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፭፥ ቍ. ፴፬-ፍ፡ም ፤ መዝሙር ፬፥ ቍ. ፪-፫ ፤ ዮሐንስ፡ ም. ፱፥፩-ፍ፡ም ።  የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ጌታ ኢየሱስ “እኔ የማያዩት እንዲያዩ፣ የሚያዩት እንዲታወሩ እኔ ወደዚኽ ዓለም ለፍርድ መጣኹ” ሲል ያስሰማናል። መዝሙረ ዳዊት “ልባችኹን እስከመቼ ታደነድናላችኹ?” እያለ ይጠይቃል። በሐዋርያት ሥራ ላይ ቅዱስ ሉቃስ ጴጥሮስና ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደኾነ በማስተማራቸው እንደተገረፉ ይነግረናል። ቅዱስ ጳውሎስም ለቆሮንቶስ ምእመናን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ከተገደለው ከኢየሱስ ክርስቶስ በስተቀር ሌላ አንዳችም ነገር እንዳልሰበከላቸው ሲያስታውሳቸው ሰምተነዋል። የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ መልእክትም “ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደኾነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?”  ብሎ ይጠይቀናል፤ ያጠይቀንማል። ያሬዳዊው መዝሙርም ጊዜው ዘመነ አስተምህሮ መዝሙሩም እሑዱ “መጻጕዕ” እንደሚባል መዝሙሩም በዮሐንስ ወንጌል የተነበበውን ምንባብ “ይቤሉ እስራኤል ኢሰማዕነ ወኢርኢነ እም አመተፈጥረ ዓለም ዘዕውሩ ተወልደ” (ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ዕውር ኾኖ የተፈጠረውን ሰው ዓይኖች ያበራ ሰው አላየንም አልሰማንም አሉ” እያለ ያዜማል።  በዐቢይነት የምናያቸው ሦስት ነጥቦች ማንሣት እወድዳለኹ፤ የደነደነ ልብ፣ የታወረ ዐይን፣ የተሰቀለ መሢሕ።      የደነደነ ልብ  በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከፍ ያለ ስፍራ ተሰጥቷቸው ከምናገኛቸው ቃላት ውስጥ ልብ አንዱ ነው። የግሪኮሮማን ሥልጣኔና ቃላት ከመግነኑ በፊት በነበረው የሴማውያን ባህል ልብ የሚለው ቃል ማወቅን፣ መረዳትን፣ ማስተዋልን ያመ...

በእርሱ ኾናችኹ ተሞልታችኋል

ምስል
  “በእርሱ ኾናችኹ ተሞልታችኋል” ( ቆላ. ፪፥ ቍ. ፲-፲፮ ፤  ፩ዮሐ፡ ም. ፪፥ ቍ. ፳፭-ፍ ፤ ሐዋ፡  ፳፪፥ ቍ. ፯-፳፪ ፤ ማቴ ፪፥  ቍ. ፳፪-ፍ፡ም) ባለፈው ሳምንት ልደትን፣ ትናንት ደግሞ ግዝረትን አከበርን። ምንባቦቹ ይኽንን ይዘው የነቢያት ትንቢት መፈጸሙን፣ ጌታ በሥጋ መገለጡን፣ ለቤተ ክርስቲያንም ጸጋውን ማደሉን ይነግሩናል። እኛንም ይኽን እንዲያው የተሰጠንን ጸጋ ታላቅነት እንድናስተውለው፣ እንድንኖረው ያሳስባሉ። ሦስት ነጥቦችን እናንሳ፦   የእመቤታችን ዝምታ (የቤተክርስቲያን ሌላኛው ሥርዓተ አምልኮ) የቤተ ክርስቲያን አምልኮ ሲባል ብዙዎቻችን የምናስበው እንደከበሮና ጸናጽል ያሉ የሙዚቃ መሣሪያዎቻችንን ወይም የሰዓታትና የማሕሌትን ያሬዳዊ ዜማን ይኾናል። ስሕተትም አይደለም። ነገር ግን የቤተ ክርስቲያን አምልኮ ድምፃዊ ብቻ አይደለም። ቤተ ክርስቲያን ኖሮዋ ኹሉ አምልኮ ስለኾነ ድምፅ በማታወጣበት ጊዜም አምልኮዋ አይቋረጥም። ይኽ አምልኮም በእመቤታችን ዝምታ ውስጥ የሚከናወን ነው። እንዴት? ወዳነበብነው የማቴዎስ ወንጌል እንኺድ። ጌታ ኢየሱስ “በነቢያት ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ” በማለት ከልደት እስከ ጥምቀት የነበረውን በእመቤታችን የድንግል ማርያም ዝምታ ውስጥ ብቻ እንድናስተውለው የተሰጠንን የጌታችንን የልጅነት፣ የጉርምስና እና የወጣትነት እድሜ ይጠቁመናል። የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ኾነ፤ በየጥቂቱ አደገ። ከእናቱ ዕቅፍ እስከ ጉልምስና ለቤተሰቦቹ እየታዘዘ አደገ። የቤተ ክርስቲያን ሊቱርጊያ የጌታችንን ሕይወት እየተከተልን ወደ ጥምቀት እንድንኼድ እየጋበዘን ነው፣ በጽሙና፣ በአርምሞ፣ የተሰጠንን እንድናስተውል እየተጋበዝን ነው። ለምን?...

ንስሐ ግቡ

ምስል
  “ኢየሱስ 'መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ።' እያለ ይሰብክ ጀመረ።” ማቴ. 4፡ 17 ንስሐ ግቡ! = μετανοεῖτε! = ዓላማን፣ ሐሳብን፣ አስተያየትን መቀየር ይህ የጌታችን ስብከት ለአይሁድ መሰበኩ የሚገርም ነው። የእግዚአብሔር ምርጥ ሕዝብ፣ ርስቱ ነኝ ብሎ የሚያስብና ለሚመካ ሕዝብ “ንስሐ ግባ!” የሚል ድምፅ አስደንጋጭ ነው። ምን ያኽል ከእግዚአብሔር ርቆ እንደሚኖር ያሳያልና። እስራኤል እንዴት እዚኽ ደረሱ?  አስተሳሰባችኹን ቀይሩ! ኢሳ. 55፡ 9 “ሐሳቤ እንደሐሳባችኹ፣ መንገዴም እንደመንገዳችኹ አይደለም”  ንስሐ የኃጢኣት ሪፖርት አይደለም!  ዓለምን፣ ሕይወትን፣ እውነትን የምናይበትን መንገድ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ማድረግ እንጂ። ለምን?  አስተሳሰባችን ካልተቀየረ ኑዛዜ አይጠቅመንም። እግዚአብሔር የማያውቀው የኑሯችን ክፍል አለን?  (ታዲያ የኑዛዜ ዓላማው ምንድነው? የኑዛዜ ዓላማው ከተሰለፍንበት ውጊያ እየከዳን የምንሸራተትበትን የኑሯችንን ስፍራ መለየት እንድንችል፣ ጉዟችን የውጊያ ነውና በውጊያው ላይ የሚያቆስሉንን የጠላት ፍላጻዎች በጥንቃቄ እንድንለይ፣ ዛሬ ያቆሰለን ነገ እንዳይገድለን እንድንጠነቀቅ፣ በኃጢኣት በመሰነካከላችን በሚመጣው የሰይጣን ክስ የተነሣ በብቸኝነት ተስፋ ቆርጠን እንዳንደርቅ፣ “እግዚአብሔር ይፍታሕ” በሚለው በካህኑ አንደበት ከቤተክርስቲያን የሚወርደውን የእግዚአብሔር ምሕረት እየጠጣን ለምልመን እንድንኖር ነው።) አስተያየታችኹን ቀይሩ! “መሃይምነት የጨለማ ጉዞ ነው!” ይሉ ነበረ፣ መሃይምነት ምን ማለት እንደኾነ ያላወቁ የ1960ዎቹ “ምሁራን”። እንደርሱ ፎክረው ጀምረውም ማኅበረሰባቸውን ፊደል በፊደል አጥለቀለቁት ግን ፊደል ቋንቋ መጻፊያ ጥበብ እንጂ እንጂ ብርሃን አይደለ...

የዓለሙን ኃጢኣት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ

ምስል
“እነሆ! የዓለሙን ኃጢኣት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።” ዮሐ. 1፡17  ክርስቲያናዊ ሰማዕትነትና ፖለቲካ ባለፈው ሳምንት ካነበብነው ሮሜ 13 ጋር ይቃረናልን? ጳውሎስ ሰበከን፤ ዮሐንስ መጥምቁ አሳየን።  ክርስቲያኖች በጎ ከሚሠሩና በጎ ኅሊና ካላቸው ጋር ኹሉ በመተባበር ንቁ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያደርጋሉ። ነገር ግን፣ ይኽ ተሳትፏቸው በኹለት መርሖች ላይ ይመሠረታል።  ሀ. የሰው ልጅ ከፈጣሪው ተነጥሎ ሊታሰብ አይችልም። የታሪክ አጋጣሚ የወለደው ወለፈንዴ አይደለም። (ማርክሲዝም፣ ሂዩማኒዝም፣ ኢንላይተንመንት፣ ወዘተ.)   ለ. ህላዌ ስጦታ ስለኾነች ማኅበረሰብ ማኅበረሰብ ከተፈጥሯዊ የሞራል ሕግ ተቃርኖ መቆም አይችልም። ልቁም ቢል ራሱን ያጠፋል።  የዮሐንስ ምስክርነት እነዚኽ ላይ የተመሠረተ ነበረ። ምስክርነቱም እስከመጨረሻው የሕይወቱ ጠብታ ድረስ ነበረ። ለምን? ምክንያቱም የዓለም ችግር በእግዚአብሔር መገኘትና በኃጢኣት መወገድ እንጂ በፖለቲካዊ ሥርዓት፣ በኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ በቴክኖሎጂ ምጥቀት አይፈታም። ዞሮዞሮ መዝጊያው ሞት ነው። ከሜሶጶጣሚያ እስከ ሮም፣ ከሮም እስከ አሜሪካ ታሪኩ አንድ ነው። ፕሌቶም ታሪክም በግልጽ ይኽን አዙሪት ይነግሩናል። ከታሪክ የምንማረው ያፈጠጠ እውነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስም የመጀመሪያው ከተማ ሠሪ ቃየን እንደኾነ ይነግረናል።  ስለዚኽ ዮሐንስ “ሄሮድስ ኤዶማዊም ቢኾን ከሮማውያን ይልቅ ዘሩ ለእኔ ይቀርበኛል” ብሎ በዘረኝነት ዐይኖቹን አላሳወራቸውም። ዛሬ ማተብ አሥረው፣ መስቀል ጨብጠው፣ “የእኛ ዘር ጥራቱ፣ ምጥቀቱና ሥልጣኔው!” እያሉ ሲያስቡና ሲናገሩ የሚውሉ ሰዎች ዮሐንስ ይመሰክርባቸዋል። እርሱ የሰው ልጅን ኑሮ ያከፋው የኃጢኣት ጨለማ እንደኾነ ያውቃል። የሰው ልጅ የችግሩ ኹሉ ...

ቤተ ክርስቲያንና ግለሰባዊነት

ምስል
 የዕለቱ ግጻዌ  ምንባቦች፦ ማቴ. 23፡23፣ ዕብ. 11፣ ራእ. 6፣9 እና ሐዋ 19፡1-6  እስመ ተዘከረ ዘይትኀሠሥ ደሞሙ መዝ 9፡17 “ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይኾኑ” ዕብ 11፡39 ዛሬ የዮሐንስ አባት ዘካርያስ እና የሙሴ መታሰቢያቸው ነው። ለምን ይታሰባሉ? ምክንያቱም በዘለዓለማዊው የሥላሴ ሕይወት ውስጥ ሕይወት ያገኘን አንድ ቤተሰብ፣ አንድ ቤተ ክርስቲያን ነን።  “ያለእኛ” = ቤተ ክርስቲያንና የሰው ልጅ የጋራ ዕጣ (ቤተ ክርስቲያንና ግለሰባዊነት)  ነቢያቱ፣ በእምነት የተመሰከረላቸው፣ ስንት ድንቅና ተአምር የሠሩት፣ ስለ እርሱ ብለው መከራ የተቀበሉትን ያለ እኛ ፍጹማን አልኾኑም። ተስፋቸው የተፈጸመው፣ ትንቢታቸው የሠመረላቸው ቃል ሥጋ ሲኾን፣ የእግዚአብሔር አብ መንፈስ በልጁ በጌታ ኢየሱስ በኩል ለቤተ ክርስቲያን ተሰጥቶ፣ ሰዎች እግዚአብሔርን ዐውቀው፣ ወድደውና ተከትለው ሲኖሩ ነው። ቃል ሥጋ እስኪኾን፣ ቤተ ክርስቲያንም በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ተሞልታ እስክትገለጥ ድረስ፣ እኛ እስክንመጣ ድረስ፣ ነቢያቱ እኛን ይጠብቁ ነበረ።  እነሆ እኛም “ስለእግዚአብሔር የሚገደሉ የእግዚአብሔር ምስክሮች” ቁጥር እስኪሞላ ድረስ ጌታችንን እንጠብቃለን። ለምን? ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር የሰውልጆችን በአምሳሉ ስለፈጠራቸው አንድ ሲኾኑ ብዙ፣ ብዙም ሲኾኑ አንድ ናቸውና። አንድ ሥጋ ናቸው። በኃጢኣት የተነሣ በዓለሙ ላይ ዛሬ ይኽ አይታይም፤ ሊታይም አይችልም። ሺሕ ጊዜ በመንደር ኾነ፣ በዓለም ዐቀፍ ደረጃ በሺሕ ዓይነት መንገድ ሲደራጅ ቢኖርም በኃጢኣት የወደቀው ዓለም አንድ መኾን አልቻለም። ምክንያቱም የበሽተኞች መደራጀት ጤንነትን አይፈጥርም።  በአንጻሩ፣ ቤተ ክርስቲያን ከዚኽ የሰው ልጅ እንደ ግለሰብም እንደማኅበረሰብም ተያይዞ ...

“አባት ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።” ዮሐ. 3፡ 37

ምስል
 የዕለቱ ግጻዌ ምንባቦች፦  ኤፌ 5፡ 21 ፤ ራእ 21፡ 1 ሐዋ 21፡ 31 መዝ 127፡ 2 ዮሐንስ 3፡ 25    “አባት ልጁን ይወዳል ሁሉንም በእጁ ሰጥቶታል።” ዮሐ. 3፡ 37 ዛሬ የሰማናቸው ምንባቦች በሙሉ (ከሐዋርያት ሥራ በስተቀር) “ሙሽራ” “ሙሽሪት”፣ ባል፣ ሚስት የሚል ቃል አላቸው። የዕለቱ መዝሙርም “ ትዌድሶ መርዓት ” (ሙሽሪቱ ታወድሰዋለች [ሙሽራዋን]) ይባላል። ዮሐንስ መጥምቅ “ሙሽራዪቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው” ሲል፣ ዮሐንስ ባለራእዩ “ወደዚኽ ና፣ የበጉን ሚስት ሙሽራዪቱን አሳይኻለኹ” የሚል ድምፅ ከመሪው መልአክ መስማቱን ይነግረናል። ቅዱስ ጳውሎስም “ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እንደወደዳት… ስለእርሷ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ” ሲል ሰምተነዋል። ስለዚኽ ሙሽርነት ለመነጋገር ግን መነሻው ነጥብ ከላይ የጠቀስነው እውነት ነው። “አባት ልጁን ይወዳል፤ ኹሉንም በእጁ ሰጥቶታል።” ሦስት ነጥቦችን እናንሣ፦   የሙሽርነት መጀመሪያ  እግዚአብሔር አብ ልጁን በፍጹም ፍቅር፣ በፍጹም ልግስና ይወድዳል። ስለዚኽም እርሱ በአባትነቱ፣ በእግዚአብሔርነቱ ያለውን ኹሉ አምላክነቱን፣ ብርሃንነቱን፣ ሕይወትነቱን ያለ አንዳች ንፍገት፣ በፍጹም ልግስና ሰጠው። አብ ለወልድ ያልሰጠው አንዳችም ነገር የለም፤ እውነተኛ አባት ነውና። ከልግስናው ብዛት የተነሣም በልጁ በኩል የእርሱን ሕይወት የሚወርስ ፍጥረትን መፍጠር ወደደ። ወድዶም በቃሉ ካለመኖር ወደ መኖር አመጣት፤ ከእርሱ ሕያውነት የተነሣ ከዘለዓለም ሕያው በኾነው ልጁ በኩል የእርሱን ሕይወት ወርሳ የምትኖር፣ የሰው ልጅ ራሷ፣ ጉልላቷ የኾነላት ፍጥረትን በአንድ ልጁ አበጀ። በልጁ፣ ለልጁ ስላበጃት፣ የልጁን ሕይወት ወርሳ የምትኖር ስለኾነችም የልጁ ትዳር፣ የልጁ ሙሽ...

“አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ።”

ምስል
  ፩ ቆሮ፡ ም. ፲፥ ቍ. ፩-፲፬ ራእየ፡ ዮሐ፡ ም. ፲፬፥ ቍ. ፩- ፮ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፬፥ ቍ. ፲፱-፴፩  ማቴዎስ፡ ም. ፲፪፥ ቍ.፩-፳፪ “ወኵሉ፡ ይሴፎ፡ ኪያከ”  “አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ።” ይኽ ቃል ከኢሳይያስ 42፡1-6 ድረስ ይገኛል።  ተስፋ ምንድነው?  ተስፋ በሚታወቅ ነገር ላይ የሚኖር መተማመን ነው።  Ἐλπίς ( ኤልፒስ) የሚለው የግሪኩ ቃል መተማመን የሚል ፍቺም ይይዛል። በማይታወቅ፣ ባልተቀመሰ፣ ምልክቱ ባልታየ ነገር ላይ ተስፋ አይደረግም። የማያውቀውን፣ ያልቀመሰውን፣ ምልክቱን ያላየውን ነገር ይኾናል ብሎ የሚተማመን ሰው “የቅዠት ባለቤት” እንጂ “የተስፋ ሰው” አይባልም። ቅዠት የካርል ማርክስ Classless Society ኾነ፣ የፕሌቶ Republic፣ ወይም የአክራሪ ካፒታሊስቶች Free Market Economy እውን የማይኾኑት የቢኾን ዓለም ቅዠቶች እንጂ ተስፋ ስላልኾኑ ነው። በብሉይ ኪዳን የነበረው የእግዚአብሔር ሕዝብ፣ የእግዚአብሔርን ማዳን ከአባቶቹ ሰምቷል፤ የእስራኤል ለቃልኪዳኗ አለመታመን የእርሱን (የእግዚአብሔርን) ታማኝ አፍቃሪነት ሳያስቀረው ምድረ ርስት ከነዓንን አውርሷቸው እንደነበረ ያውቃል፤ ይኽ በጭላንጭል የሚያውቀው የእግዚአብሔር ታማኝነት የተስፋው ምሶሶ ነበረ። ስለዚኽም፣ በነበረበት ውስጣዊ ፖለቲካዊ ምስቅልቅልና የሮማውያን ቅኝ ግዛት ውስጥ ኾኖም ነቢያቱ “የተቀጠቀጠውን ሸምበቆ የማይሰብረው፣ የሚጤስን ጧፍ የማያጠፋው፣ የእግዚአብሔር ምርጥ ብላቴና፣ እግዚአብሔር የቀባው መሢሑ ይመጣል!” እያለ ተስፋ የሚያደርግ፣ የተስፋ ሕዝብ ነበረ።  ተስፋ ዘላቂ መፍትሔ ላይ ያረፈ ዓይን ነው። በጥንታዊ ግሪክ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ከማይገኙ ቃላት መካከል አንዱ ተስፋ ነው ይባላል። ም...