ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መብዛት፣ መጾም እና መቀደስ

ምስል
  “ከፊት ይልቅ ትበዙ ዘንድ በጌታ በኢየሱስ እንለምናችኋለን።” ኤፌ 4፡ 11 “ περισσεύητε” ፩ ተሰ ም. ፬፥ ቍ. ፩-፲፫ ፤ ፩ ጴጥ፡ ም. ፩፥ ቍ. ፲፫-ፍ፡ም ፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፲፥ ቍ. ፲፯-፴ ፤ መዝሙር፡ ፺፭(፺፮)፥ ቍ. ፭-፮። ማቴዎስ፡ ም. ፮፥ ቍ. ፲፯-፳፭ የዐቢይ ጾም ኹለተኛ ሳምንት ላይ ነን። ሳምንቱ ቅድስት ይባላል። ከዚኽ ሳምንት ጀምሮ እስከ ሆሳዕና ድረስ ያለው ጊዜ "ጾመ አርብዐ"፣ "ጾመ ኢየሱስ" ይባላል። ለዚኽ እሑድ የተመደቡት ምንባቦች ኹሉም ቅድስና ምን እንደኾነ፣ ለሰው ልጅ ምን ያኽል አስፈላጊ እንደኾነና የቅዱስ ሰው ኑሮም ምን መልክ እንዳለው ይናገራሉ። መዝሙረኛው “ምሥጋናና ውበት ሰማያትን በሠራው በእግዚአብሔር ፊት፣ ቅድስናና ግርማም በመቅደሱ ውስጥ እንደኾኑ” ይዘምራል። ጌታ ኢየሱስም “ስትጾሙ እንደግብዞች አትኹኑ!” እያለ የእግዚአብሔር ሕዝብ ጾም ምን እንደሚመስል ያስተምራል። ቅዱስ ጳውሎስ “የእግዚአብሔር ፈቃድ የእናንተ መቀደስ ነው” ይላል። ቅዱስ ጴጥሮስ “በኑሯችኹ ኹሉ ቅዱሳን ኹኑ” ይላል። የሐዋርያት ሥራ ጸሐፊው ቅዱስ ሉቃስም በምጽዋቱና በጸሎቱ የሚታወቀው መቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ ቅድስናው ይጨምር ዘንድ ጴጥሮስን 40 ማይል ገደማ ርቃ ከምትገኘው ከኢዮጴ ልኮ ሲያስመጣ ሰምተናል። ጾመ ድጓውም “ሰንበትየ ቅድስትየ” እያለ ሰንበትን ከማሞካሸት በተጨማሪ “ተፋቀሩ፡ በምልዓ፡ ልብክሙ። አክብሩ፡ ሰንበተ፡ በጽድቅ፡ ዝግቡ፡ ለክሙ፡ መዝገበ፡ ዘበሰማያት፡ ኀበ፡ ኢይበሊ፡ ወኢይማስን” (በፍጹም ልባችኹ ተፋቀሩ። ሰንበትን በጽድቅ አክብሩ። በሰማያትም ብል የማይበላውና የማይጠፋ ሀብትንን ሀብትን አከማቹ) እያለ እነዚኽኑ ምንባቦች ይዘምራል። እነዚኽን ኹሉ ምንባቦች መብዛት፣ መጾም እና መቀደስ በሚሉ ሦ...

“መንገዱ”

ምስል
የዛሬ ምንባቦች፦ ሮሜ 1፡1-12፣ 1ኛ ጴጥ. 1፡ 13-22፣ ሐዋ 19፡ 1-11 መዝ 47፡7 ፣ ሉቃ 2፡ 36-42 መዝሙር፦ ተወልደ ኢየሱስ የአስተንትኗችን መነሻ ሐዋ 19፡9 ላይ የሚገኘው “መንገዱ” የሚል ቃል ነው። ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ላይ ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን ከተማ በነበረበት ጊዜ ሲያስተምር አንዳንድ ሰዎች “እልኸኞች ኾነው በሕዝብ ፊት መንገዱን” እንደሰደቡ ይነግረናል። የጥንት ክርስቲያኖች “ራሳቸውን የመንገዱ ተከታዮች” ብለው ይጠሩ ነበረ። የኑሮ ዘይቤያቸውንም “መንገዱ” በግሪክ ὁδὸσ ፣ በሱርስት ደግሞ ܐܘܪܚܐ ፣ በዕብራይስጥ הדרך እያሉ ይጠሩት ነበረ። ስለዚኽ መንገድ ሦስት ነጥቦችን እናንሳና ምንባቦቻችን ምን እያሉን እንደኾነ እንመልከት፦   በእምነት የመታዘዝ መንገድ  ይኽ መንገድ ምን ዓይነት መንገድ ነው ብለን ስንጠይቅ መልሱን ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ ላይ “ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ” ሲል ይመልስልናል። የራሱን ማንነት ለሮሜ ክርስቲያኖች ሲያስተዋውቅም “በአሕዛብ ኹሉ መካከል ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን” ይላል።  በሌላ አባባል፣ አሕዛብን ኹሉ አምነው እንዲታዘዙ ማድረግ የቤተክርስቲያን ቋሚ ሥራዋ እንጂ ሌሎች አካላት እስኪ የአካታችነት (inclusivity) ፖሊሲ ስለቀረጹ፣ ወይም እነእገሌ እነ እገሌንም ያካተተ የስብከት መርሐ ግብር አዘጋጂ ስላሏት አይደለም። ክርስቲያኖች የሚኖሩለትም፣ የሚኖሞቱለትም ሌላ ዓላማ የላቸውምና። በእምነት መታዘዝ መጀመሪያ እምነት ይጠይቃል። የሰው ልጅ በተፈጥሮው አማኝ ፍጥረት ነው። ዕውቀቱ ፍጹም ስላልኾነ ሳያምን መንቀሳቀስ አይችልም። ሌላው ቀርቶ በእግዚአብሔር አናምንም የሚሉ ሰዎች እንኳ አለማመናቸውን ባያምኑ ኖሮ የሚያደርጓቸውን ...

ይኽ ምሥጢር ታላቅ ነው! ኤፌ 5፡ 32

ምስል
  “ዐቢይ ውእቱ ዝ ነገር!”/ “ይኽ ምሥጢር ታላቅ ነው!”/ “τὸ μυστήριον τοῦτο μέγα ἐστίν” ኤፌ 5፡ 32  የትኛው? ሦስት ነጥቦችን ላንሣ፦  እግዚአብሔር ፍጥረትን የወደደበት ዘለዓለማዊ ምሥጢር  ከልግስናው፣ ከደግነቱ፣ ከአፍቃሪነቱ ብዛት ህልውና ያልነበረውን ዓለም ካለመኖር ወደመኖር አመጣው፤ ፍጥረትን ኹሉ ወክሎ ሲጠራ አቤት ብሎ ለተወደደበት ፍቅር ምላሽ መስጠት የሚችል የሰውን ልጅም በፍጥረቱ ላይ ጉልላት አድርጎ አኖረ። ይኽን ያደረገበት ምክንያትም የፍጥረት ራስ የኾነው የሰው ልጅ እግዚአብሔር ፍጥረትን ለወደደበት ዘለዓለማዊ ፍቅር የፍቅር ምላሽ በመስጠት ከእርሱ ከእግዚአብሔር ጋር በፍቅር አንድ አንድ ኾኖ እንዲኖር ነው። በዚኽ አንድ በኾነበት ፍቅርም የእግዚአብሔር ብቻ የኾነው ሕያውነት ኹሉ የሰው ልጅ ሀብት ይኾናል። ክብሩን ይለብሳል። ሕይወቱን ይወርሳል። ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ስለኾነ ከዐፈር የተበጀው፣ ህልውና፣ ሕያውነት የሌለው የሰው ልጅ ሕያው፣ ህልው ይባላል። ሕያው ኾኖም ፍጥረትን ኹሉ ሕያው ያደርጋል። ራሱ ሕያው ከኾነ አካሉም ሕያው ነውና። ይኽ ከእግዚአብሔር ለፍጥረት የተለገሰ ፍቅር ፍጹም ስለኾነ ከሰው ልጅ የሚገኘው ምላሽ ምንም ቢኾን አይለወጥም። በዚኽ ዘመነ አስተርእዮ በቤተ ክርስቲያን የምናስበው፣ የምናመልከውም ይኽንን ዓለም ሳይፈጠር በፊት ጀምሮ የተወደድንበትና ዘመኑ በደረሰ ጊዜ በእግዚአብሔር ልጅ ሰው መኾን የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ ፍቅር ነው። ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ ለእኛ የነበረው እኛ የእርሱ ኾነን፣ እርሱም የእኛ ኾኖ የመኖሩን ዕቅድ ፈጸመው። ብንበድለው ይቅር ብሎ፣ ብንርቀው ቀርቦ የፍቅሩን ዕቅድ ፈጸመው። ዳግም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ነፋስ እንዳይገባ፣ መተጣጣት እ...