ልጥፎች

ከኤፕሪል, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ትንሣኤ ስም እና ቅድስና

ምስል
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን! በአማን ተንሥአ! የዕለቱ ምንባቦች፦ ፩ኛ፡ ቆሮ፡ ም. ፲፭፥ ቊ. ፩-፳፤ ፩ኛ፡ ዮሐ፡ ም. ፩፥ቊ. ፩-ፍ፡ም፤ ግብ፡ ሐዋ፡ ም. ፳፫፥ ቊ. ፩-፲፤ ዮሐንስ፡ ም. ፳፥ቊ. ፲፱-ፍ፡ም፤ ዮሐንስ፡ ም. ፲፯፥ ቍ. ፩-ፍ፡ም። ትንሣኤ  የበዓላት ኹሉ በኵር፣ የቤተክርስቲያን ትርጉምና ድሏ የሙሽራዋ የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው። ስለዚኽም፣ ከበዓላት ኹሉ ከፍ አድርጋ ትንሣኤን ታከብራለች። በክርስቶስ ትንሣኤ ውስጥ ያለውን ደስታ፣ ተስፋና ሕይወት በሚገባ እንድናጣጥመውም ስምንት ቀናትን እንደ አንድ ቀን ቆጥራ ስታከብር፣ እርሱም አልበቃ ብሎ እስከ ዕርገት በዓል ድረስ ያሉትን 40 ቀናት ስትጨምርበት እናያታለን። ለምን? ምክንያቱም የክርስቶስ ትንሣኤ እውነት ካልኾነ ቤተክርስቲያን ከንቱ ናት። የነቢያት ትንቢት፣ የሐዋርያትም ስብከት፣ የሰማዕታት መከራ፣ የእናንተም ጾምና ጸሎት የመቃብር ድንጋይ ደፍጥጦ በዜሮ የሚያባዛው ከንቱነት ይኾናል። ሰው ኾኖ መኖርም ትርጉም የሌለው የመከራ ቀንበር ይኾናል። ግን ክርስቶስ በእውነት ከሙታን ተነሥቷል ስለዚኽም ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፣ “ በኹሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ኹልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን። ” (2ኛ ቆሮ. 4፡8) ኹልጊዜ በጌታ ደስ ይለናል! (ፊል 4፡4)      ስም ይኽ ዛሬ ከዮሐንስ ወንጌል የተነበበው ምንባብ የጌታ ኢየሱስ የሊቀ ካህንነቱ ( כהן גדול) ( ἀρχιερεύς) ጸሎት ይባላል። ከዚኽ ጸሎት ቀጥሎ የሚመጣው የዓለሙን ኃጢኣት የሚያስወግደው የእግዚአብሔር በግ ...

“ዓለም በልጁ እንዲድን እንጂ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውም” (ዮሐ 3፡17)

ምስል
የዕውቀት ድንበር፣ ከላይ መወለድና የፍቅር ነጻነት  ምንባባት፦ ሮሜ 7፡1-19፤ 1ኛ ዮሐ 4፡ 18-ፍጻሜ፤ ሐዋ 5፡ 34-ፍጻሜ፤ መዝ 16(17)፣ 3፤ ዮሐ 3፡ 1-20።   ዐቢይ ጾም ከተጀመረ ሰባተኛ ሳምንት ላይ ደረስን። ይኽ ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል። ቤተ ክርስቲያን ኒቆዲሞስ ለተሰኘው በጌታ መዋዕለ ሥጋዌ ለነበረ መምህር የተሰጠውን ምሥጢረ ጥምቀትን የሚመለከት ትምህርት እያስታወሰች፣ ደግሞም ኒቆዲሞስ ሲጀምር በጨለማ ቢመጣም ኋላ ላይ ጌታን አምኖ ያደረገውን በጎ ምግባር እየዘከረች በጾመ ድጓዋ ሙሽራዋን በኒቆዲሞስ አንደበት “ረቢ ንብለከ፤ ነአምን ብከ” (መምህር እንልኻለን፤ እናምንብኻለንም) እያለች ትዘምራለች።  በጥንቱ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ዐቢይ ጾም ንዑሰ ክርስቲያን በፋሲካ ሌሊት ለሚካኼደው ጥምቀታቸው የሚዘጋጁበት ጊዜ ነበረ። ስለዚኽ የጥምቀት ጊዜያቸው ከመድረሱ ጥቂት ቀደም ብሎ ይኽን ምሥጢረ የሚመለከት ትምህርት መማራቸው የሚገባ ነው። ከእነዚኽ ምንባቦች ውስጥ ሦስት ነጥቦችን እናንሳና ራሳችንን እንመልከት።        የዕውቀት ድንበር  ዛሬ በምንባቦቹ ውስጥ ያገኘናቸው ኒቆዲሞስና ገማልያል የሚባሉ መምህራን በማመንና ባለማመን ድንበር ላይ ቆመው እናገኛቸዋለን። የሚያዩትን ጌታ ኢየሱስ የሚባል እውነት፣ በትምህርት ከሚያውቁትና ይኾናል ብለው ከሚጠብቁት ለማስማማት የቸገራቸው ይመስላል። ገማልያልም የሐዋርያትን ስብከት ለተቃወመው የአይሁድ ሸንጎ “ይህ ሥራ ከሰው እንደሆነ ይጠፋል፤ ከእግዚአብሔር እንደሆነ ግን ታጠፏቸው ዘንድ አይቻላችኹም” ብሎ ያሳስባል። “እንደኾነ”ን ከሥሯ እናሥምርባት። ኒቆዲሞስ ደግሞ ሰው በማያይበት፣ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ “መምህር ...